エピソード

  • የግንቦት 27 ቀን 2018፤ ዓለም ዜና
    2026/06/04
    በዛሬው የዓለም ዜና ተቃዋሚው የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በክልሉ ምርጫ«የማጭበርበር ተግባራት ተፈጽሟል» ሲል ቅሬታ ማቅረቡን።የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ)በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ የተከሰተዉ ሁከት በጥልቅ እንዳሳሰበው ማስታወቁ።በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ችላ ተብለዋል ሲል አንድ የእርዳታ ድርጅት መግለጹን።ሊባኖስ፤ የእስራኤል የድሮን ጥቃቶች መቀጠላቸውን መግለጿ።ኩዌት የኢራን ድሮን አውሮፕላን ማረፊያዋን መምታቱን ማስታወቋን።የአሜሪካ ሕግ አውጪዎች ሀገሪቱ በኢራን የምታደርገውን ወታደራዊ እርምጃ ለማስቆም የቀረበውን ውሳኔ መደገፋቸውን የሚያስቃኙ ዜናዎች የሚሉት ተካተዋል።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/06/03
    የግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን እየሰፋ መጣ ያሉትን ጥቃት የመንግሥት የፀጥታ አካላት ያላቸውን መዋቅር ተጠቅመው እንዲያስቆሙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ጠየቁ። በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኅብረቱ አባል ሃገራት ኤምባሲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ያልተካሔደባቸው የምርጫ ክልሎች ድምፅ የመስጠት «ዕድል ይሰጣቸዋል» የሚል ተስፋ እንዳላቸው አስታወቁ። ዴሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ በኢቦላ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 343 ደረሰ። ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ቀጥላለች።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • የዓለም ዜና፤ ግንቦት 25 ቀን 2018 ማክሰኞ
    2026/06/02
    -አርሰተ ዜናዎች--ሩሲያ በዩክሬን ላይ በድጋሚ በሰነዘረችዉ ከፍተኛ ጥቃት ቢያንስ አስር ሰዎች ተገደሉ ከ100 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆሰሉ።-በኢትዮጵያ የተካሄደው የሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ የድምፅ ቆጠራ ውጤት፣ በምርጫ ጣቢያዎች እየተለጠፈ ይገኛል።--በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ሀገረ ስብከት በአስኮ ወረዳ በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖች መገደላቸውን ሀገር ስብከቱ አመለከተ። የመቶ አንድ ዓመት እድሜ እንደነበረው የተገለጸው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንም ሙሉ በሙሉ በእሳት መጋየቱ ተነግሯል።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • DW Amharic የግንቦት 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2026/05/31
    የጋምቤላ ክልል ፖሊስ “የተለየ የይለፍ ፈቃድ ካልተሰጠ በቀር” ማንኛውም ተሽከርካሪ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት መንቀሳቀስ እንደማይችል አስታወቀ። በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አምስት ሕሙማን ከኢቦላ ማገገማቸውን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድኃኖም ተናገሩ። ኢራን ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው ድርድር የኑክሌር የጦር መሣሪያ ላለመስራት መስማማቷን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ። የኢራን ዋና ተደራዳሪ ሞሐመድ ባግኸር ጋሊባፍ ግን “የኢራናውያን መብቶች መከበራቸውን ሳናረጋግጥ አንዳች ሥምምነት አናጸድቅም” ብለዋል።
    続きを読む 一部表示
    8 分
  • የግንቦት 22 ቀን 2018 ፤የዓለም ዜና
    2026/05/30
    የዛሬው የዓለም ዜና፤የአማራ ፋኖ የጣለው የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ገደብ የምርጫ ሥራዉን ስለማስተጎጎሉ የደረሰው መረጃ እንደሌለ ምርጫ ቤርድ ማስታወቁ፣የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የኢቦላ ወረርሽን ወደተቀሰቀሰባት ዲሞክራቲክ ኮንጎ ማምራታቸውን፣ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ ትዕዛዝ መስጠቷን፣ በጀርመን የሙኒክ አውሮፕላን ማረፊያ አጠራጣሪ ድሮን መታየቱን ተከትሎ ለአጭር ጊዜ በረራ መቋረጡን አሜሪካ ስምምነት ላይ ካልደረሰ በኢራን ጦርነቱን እንደገና ለመጀመር ዝግጁ መሆኗን መግለጿን፣እንዲሁምሩሲያ፤ በአርሜኒያ የሚገኙ አምሳደሯን መጥራቷን አካቷል።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    2026/05/29
    ከአማራ ክልል መንገደኞችን ጭኖ ትናንት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ አውቶብስ ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካቶች መገደላቸው ተሰማ። ማዕከላዊ ኬንያ ውስጥ በሚገኘው የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት የተነሳውን እሳት በመለኮስ የተጠረጠሩ ስምንት ተማሪዎች መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የኬንያ ፍርድ ቤት በሀገሪቱ በኤቦላ ተሐዋሲ ለተያዙ የአሜሪካ ዜጎች አግልሎ ማቆያ የማዘጋጀት እቅድን በጊዜያዊነት አገደ። ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ለገባችበት ውዝግብ ለታሰበው የሰላም ስምምነት ከቃል ይልቅ ተግባር እንደምትፈልግ አስታወቀች።
    続きを読む 一部表示
    11 分
  • DW Amharic የግንቦት 20 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    2026/05/28
    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በጥሞና ወቅት “ፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ” ከለከለ። ክልከላው የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያግዛል በተባለው የጥሞና ጊዜ ከማይደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተካተተ ነው። ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚዋጋው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል “ለተከታታይ አምስት ቀናት ከአንቡላንሶች በስተቀር ሁሉም መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ መደረጋቸውን” አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት አገሪቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ያደረገው ውይይት ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
    続きを読む 一部表示
    10 分
  • የረቡዕ ግንቦት 19 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    2026/05/27
    አ.አ፥ ለቀጣዩ ምርጫ ሥራ ዝግ እንደሚኾን ምርጫ ቦርድ ዐሳወቀ፤ አ.አ፥ 1 ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በመላ ኢትዮጵያ ተከበረ፤ ጆሐንስበርግ፥ የጋና መንግሥት ዜጎቹን መጤ ጠል ሥጋት ካጠላባት ደቡብ አፍሪቃ ወደ አገራቸው እየመለሰ ነው፤ ዋሽንግተን፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ናይሮቢ፥ ካናዳ እና ባሐማ ከኤቦላ ጋር የተገናኘ የጉዞ ክልከላ ተግባራዊ አደረጉ፤ ጋዛ፥እሥራኤል አዲስ የተሾሙ የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አዛዥን መግደሏን ዐሳወቀች፤
    続きを読む 一部表示
    10 分